የሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ስልጣን እና ተግባር
የሴቶች፣ ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ስልጣን እና ተግባር
- በክልሉ ውስጥ የሴቶች፣ ህፃናት፣ አረጋዊያን እና አካል ጉዳተኞች መብቶችና ጥቅሞች ለማስከበር የሚረዱ የፖሊሲ ሃሣቦችን ያመነጫል፣ የማስፈፀሚያ ስልቶችን በመቀየስ ለተግባራዊነታቸው አስፈላጊውን ክትትል ያደርጋል፤
- በሴቶች፣ በህፃናት፣ በአካል ጉዳተኞች እና በአረጋዊያን መብቶች ዙሪያ የተደነገጉ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና አገራዊ ስምምነቶች በክልሉ ተፈጻሚ ስለመሆናቸው ክትትል ያደርጋል፣
- ብሄራዊ የሴቶች ፖሊሲ፣ የማህበራዊ ጥበቃ ፖሊሲ እና የህጻናት ፖሊሲ ተግባራዊ እንዲሆን በክልሉ ውስጥ የሚካሄዱ ጥረቶችን ያስተባብራል፤
- በክልሉ መንግሥት አካላት የሚዘጋጁ ፖሊሲዎች፣ ሕጎች፣ የልማት ፕሮግራሞች፣ ፕሮጀክቶችና ሪፖርቶች የስርዓተ-ጾታን፣ ህጻናትን፣ አረጋዊያን እና አካል ጉዳተኞችን ጉዳይ ለማካተት የሚያስችላቸውን ስልት በመንደፍ አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ ያደርጋል፣ በሂደትም የሴቶችን፣ ህጻናትን፣ አረጋዊያን እና አካል ጉዳተኞችን ተሣትፎና ተጠቃሚነት ያረጋግጣል፤
- በሴቶች፣ ህጻናት እና አካል ጉዳተኞች ላይ የሚቃጡ መድሎዎችን፣ ጥቃቶችን እና የሚፈፀሙ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን በጥናት በመለየት እነዚሁ የሚወገዱባቸውን የመፍትሄ ሃሣቦች ያመነጫል፣ አፈፃፀማቸውን ይከታተላል፤
- ልዩ ፍላጎት ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎችን በተመለከተ በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን የተዛባ አመለካከት ለመቀየር የሚያስችል ቀጣይነት ያላቸው የግንዛቤና የንቅናቄ ስራዎችን ያከናዉናል፣
- በህፃናት ላይ የሚፈፀሙ ህገ-ወጥ ዝውውርና ፍልሰት፣ የጉልበት ብዝበዛ እና ሌሎች የመብት ጥሰቶችን ለመከላከል የሚረዱ የአሰራር ሥርዓቶችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ይዘረጋል፣
- ሴቶች ለዘመናት በበታችነትና በልዩነት ከመታየታቸው የተነሳ የደረሰባቸውን ተፅዕኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ረገድ ተሣትፏቸውን ለማሳደግ ልዩ ትኩረትና ድጋፍ መስጠት ስለሚቻልበት ሁኔታ ለክልሉ መንግሥት ሃሣብ ያቀርባል፣ አተገባበሩን ይከታተላል፤
- ሴቶችና አካል ጉዳተኞች በክልሉ ውስጥ የስራ፣ ቅጥር፣ የስልጠና እና የደረጃ እድገት እድሎች ሆነ እነዚሁ ለማስፈጸም በሚደራጁ የተለያዩ ኮሚቴዎች ውስጥ በሚገባ ስለመወከላቸው ይከታተላል፣
- የተለያዩ የክልሉ መንግሥት አካላት ሴቶችን በውሣኔ ሰጭነት ቦታዎች በመመደቡ ረገድ በቂ ትኩረት ስለመስጠታቸው ይከታተላል፤ብቃት ያላቸውን ሴቶች እየለዩ በየደረጃው ለሚገኙ ወሳኝ አካላት ያቀርባል፣
- ሴቶች፣ ህጻናት፣አረጋዊያን እና አካል ጉዳተኞች እንደየ ችግሮቻቸው አይነት በነጻ ፍላጎታቸው ተደራጅተው ለመብቶቻቸውና ለጥቅሞቻቸው መከበር እንዲታገሉና
- በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ፣ በመልካም አስተዳደርና በልማት እንቅስቃሴዎች ውስጥ በሙሉ አቅማቸው እንዲሳተፉና ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ ሁለንተናዊ ድጋፍ ያደርጋል፣ በየተቋቋሙበት አግባብ ተግባራቸውን እየተወጡ ስለመሆኑም በቅርብ ይከታተላል፤
- በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙትን ሴቶች፣ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች እና ሌሎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሚረዱ ጥናቶችን ያካሂዳል፣ እንዲጠኑ ያደርጋል፣ ፕሮግራሞችንና ፕሮጀክቶችን በመቅረፅ ተግባራዊ ያደርጋል፣ በዚሁ ዓላማ ላይ ተመስርተው ለሚንቀሳቀሡ ድርጅቶች አስፈላጊውን እገዛ ያደርጋል፤
- ስርዓተ-ጾታን በሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች፣ ከተለያዩ የማህበረ-ሰብ ተቋማትና ከራሣቸው ከሴቶች ማህበራት ጋር ተባብሮ ይሰራል፤
- የጾታ እኩልነትን ለማስፈን፣ በተለያዩ እንቅስቃሴዎች ውስጥ የሴቶችን ተሣትፎ ለማጎልበትና ህብረተ-ሰቡ በሴቶች ላይ ያለውን የተሣሣተ ግንዛቤ ለመቀየር የሚረዱ ስልጠናዎችንና ዓውደ-ጥናቶችን ያካሂዳል፣ ውጤቶቻቸውንም ይገመግማል፤
- የአረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞችን እና ሌሎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ፍትሀዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚረዱ ስልጠናዎችንና ዓውደ-ጥናቶችን ያካሂዳል፣ ውጤቶቻቸውንም ይገመግማል፤
- ሴቶችን፣ አረጋዊያንን እና አካል ጉዳተኞችን ለሚያግዙና ለክልሉ ዘላቂ ልማት አስተዋጽኦ ለሚያደርጉ ፕሮግራሞችና ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የሚውል ሀብት ያፈላልጋል፣ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆንም ድጋፉ የአነዚህን የህብረተሰብ ክፍሎች ህይወት ለማሻሻል ስለመዋሉና ውጤታማ ስለመሆኑ ይከታተላል፤
- አግባብ ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የቤተሰብና የህፃናት መብትና ደህንነት እንዲጠበቅ ለማድረግና የጋብቻ ስርዓትን ለመንከባከብ የወጡ ፖሊሲዎችን ተግባራዊ ያደርጋል፤
- ሴቶችን፣ ህጻናትን፣ አረጋዊያንን፣ አካል ጉዳተኞችን እና ሌሎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ማዕከል አድርገው የሚሰሩ የተለያዩ አካላትን
- የተግባር ዕቅድና አፈፃፀም ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣ ቅንጅታዊ አሰራር እንዲኖራቸው ያስተባብራል፤
- የሀገሪቱ ማህበራዊ ጉዳይ ፖሊሲዎችና ህጎች በክልሉ ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆኑ ያደርጋል፣
- ዝርዝሩ ይህንን አዋጅ ለማስፈፀም በሚወጣ ደንብ የሚወሰን ሆኖ በስራ ላይ ያሉትን የአረጋዊያን፣ የአካል ጉዳተኞች፣ የህጻናትና ሌሎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ድጋፍ፣ ተሀድሶና እንክብካቤ ማዕከላት ያስተዳድራል፣ በክልሉ ውስጥ በተለያዩ አካባቢዎች እንደተገቢነታቸው መሰል ማዕከላትና ድርጅቶች እንዲቋቋሙ ያደርጋል፤ የማህበራዊ ኑሮ ጠንቆች ይወገዱ ዘንድ የክልሉን ህብረተሰብ ሁለንተናዊ ጥረት ያስተባብራል፣ እንደ ሴተኛ አዳሪነትና ጎዳና ተዳዳሪነት ባሉ አስከፊ ችግሮች ላይ የወደቁ ወገኖችን ያቋቁማል፣ ያደራጃል፣ ይደግፋል፡፡
- አግባብ ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት ለከፋ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች የሚጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ተገቢውን የድጋፍ አገልግሎት እንዲያገኙ አማራጭ የድጋፍ ስልቶችን ይቀይሳል፣ ተጋላጮችን ይለያል፣ ድጋፉን ያስተባብራል፣
- በገጠር ሆነ በከተማ የሴፍቲኔት ፕሮግራም ውስጥ በቀጥታ ተጠቃሚ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን መረጃ ይለያል፣ ያደራጃል፣ ለተጠቃሚነታቸው ከሚመለከታቸው አካት ጋር በቅንጅት ይሰራል፣
- የሴቶች፣ህጻናት እና ሌሎች የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚመለከት ዘመናዊ የመረጃ አስተዳደር ስርአት ይዘረጋል፣
- የማህበራዊ ጥበቃ ቋተ-ንዋይን ያቋቁማል፣ ውጤታማ እንዲሆን ድጋፍና ክትትል ያደርጋል፣
- የዜግነት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥርዓት እንዲዘረጋና የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር ይሰራል፣
- የሚመለከታቸውን አካላት በማስተባበር የሕፃናት መልካም አስተዳደግና ስብዕና ግንባታ፣ ድጋፍ፣ እንክብካቤ እና ተሀድሶ ላይ ለወላጆችና አሳዳጊዎች ተገቢውን ግንዛቤና ሥልጠና በመሥጠት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል፤
- በተለያዩ ምክንያቶች ለችግር የተጋለጡና ወላጆቻቸውን ያጡ ሕፃናት ጉዲፈቻን ጨምሮ በሀገር ውስጥ ባሉ አማራጭ ድጋፍና እንክብካቤ ዘዴዎች ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ስልት ይቀይሳል፣ ተግባራዊ ያደርጋል፤