የአብክመ ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ መድረኩ ከሴቶች፣ ከህጻናት፣ ከአረጋውያን እንዲሁም ከአካል ጉዳተኞች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት አንጻር የተከናወኑ ተግባራትን የምንገመግምበትና የቀጣይ አቅጣጫ የምናስቀምጥበት ነው ብለዋል።
የዕቅድ አፈጻጸሙ በቢሮው የዕቅድ ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ ብርሀኑ አለሙ እየቀረበ ሲሆን በመድረኩ የመሞሪያ ኃላፊዎች፣የሴት አደረጃጀቶች ፣ የአረጋውያን ማህበር አመራሮች እንዲሁም የአካል ጉዳተኞች ፌደሬሽን አመራሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
ባህር ዳር



