Message From Bureau

የአብክመ እሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊነት ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ በእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸው ሴቶች የህብረተሰቡን ግማሽና በላይ እንደሆኑ የተለያዩ መረጃዎች ቢያመላክቱም በሁሉም መስክ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ እንዳይሆኑ የነበረውን የተዛባ የስርዓተ ፆታ አመለካከት እንቅፋት እንደሆነ በመጥቀስ ቢሮው የሴቶችን ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸው በተለያዩ ምክንያቶች ጾታዊ ጥቃት የደረሰባቸዉ ሴቶችና ሌሎች ለችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን  ሁለንተናዊ ደህንነት አጋር ድርጅቶችም ሆነ ማንኛውም አካል ለዜጎች የዜግነት ግዴታውን ይወጣ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።

የደረሰባቸዉ ሴቶችና ሌሎች ለችግር ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን  ሁለንተናዊ ደህንነት አጋር ድርጅቶችም ሆነ ማንኛውም አካል ለዜጎች የዜግነት ግዴታውን ይወጣ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።

ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ
ቢሮ ኃላፊ

The Main Sectors Of Bureau

ዜና | News

Center For The Disability

Follow Us

የአካል ጉዳተኞች ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከልማለት አካል ጉዳተኛ ዜጐችን በመቀበል በምርጫቸውና የአካል ጉዳታቸውን ታሳቢ ባደረገ መንገድ በተለያዩ የስልጠና ዘርፎች የሙያና የቴክኒክ ክህሎት እንዲኖራቸው በማድረግ በገቢ ማስገኛ ስራዎች መሠማራት በሚችሉበት አግባብ ዝግጁና በገበያ ብቁ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያሰለጥን ተቋም ነው፡፡

.በክልላችን ብቸኛ ማዕከል ሲሆን ማዕከሉ የቋቋመበት ዋና ዓላማም በብሔራዊ ክልሉ ውስጥ ለሚገኙ አካል ጉዳተኛ ዜጐች ያላንዳች ልዩነት አካላዊ ሁኔታቸውንና ፍላጐታቸውን መሰረት ያደረገ የቴክኒክና ሙያም ሆነ የክህሎት ማዳበሪያ ስልጠናዎችን በመስጠት አካል ጉዳተኞች የሚኖራቸውን በስራ ገበያ የመወዳደር አቅም ማጐልበት ነው፡፡

ክልሉ ውስጥ የሚገኙትን አካል ጉዳተኞች በመቀበል ፍላጐቶቻቸውንና ዝንባሌዎቻቸውን መሰረት ያደረገ፣ ቀልጣፋና ደረጃውን የጠበቀ ሙያዊ ስልጠናና የክህሎት ማበልፀግ አገልግሎት እንዲያገኙና በስራው ዓለም የሚኖራቸው የተወዳዳሪነት አቅም ከፍ እንዲል ያደርጋል፡፡

በሴቶች እና ህፃናት ላይ የሚፈፀም የኃይል ጥቃትን ለመከላከል እና በአንድ ማእከል ሁሉን አቀፍ  ምላሽና አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ነው፡፡

በተጠቂዎች እና በህብረተሰቡ ላይ የማይሽር ጠባሳ የሚተው፣ በሀገር ልማት ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖም የከፋ በመሆኑ የችግሩን መሠረታዊ መንስኤዎች በማወቅ ዘላቂ መፍትሄ ማምጣት በማስፈለጉ፤

ሴቶችና ህፃናት በዚህ ጥቃት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተፈፀባቸው መሆኑና ከአካላዊ፤ወሲባዊ፤ሰነ-ልቦናዊጥቃቶችበተጨማሪ ለኢኮኖሚያዊጥቃቶች ተጋላጭ ከመሆናቸው የተነሳ የፍትህ ስርዓቱን ተጠቅመው መብታቸውን ለማስከበር የተለየ ጥበቃና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ፡

በሴቶች እና ህፃናት ላይ የሚፈፀሙ የኃይል ጥቃቶችን ለማስወገድ የተለያዩ የህግ ማዕቀፎች  /አለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ስምምነቶች እና ቻርተሮች / ቢኖሩም ተግባራዊ ከማድረግ አኳያ እጥረቶች ያሉ እና ለውጥ ያልመጣ በመሆኑ

ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት፣ ለመከላከል፣ ተፈፅመው ሲገኙ ተጠቂዎች አገልግሎቱን ሳይጉላሉ በአንድ ማዕከል እንዲያገኙ በማድረግ የህክምና፣ የፍትህ እና የቀጣይ ህይወታቸው ጉዳይ እልባት እንዲያገኙ ለማድረግና ወንጀል ፈፃሚዎችን በአጭር ጊዜ ተገቢውን እርምት እንዲያገኙ በማድረግ በተቀናጀ እና ሁሉን አቀፍ በሆኑ ዘዴዎች ተከትሎ መስራት አስፈላጊ በመሆኑ የአንድ ማዕከል የተቀናጀ የእንክብካቤ እና ፍትህ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ማቋቋሙ አስፈላጊ ሆኗል፡፡

“የአካል ተሃድሶ አገልግሎት”ማለት ለአካል ጉዳተኞች አስፈላጊ የሆኑ ሰው ሰራሽ መሣሪዎችን በማሟላት የጉዳተኞችን አካላዊ ምቾት በመጠበቅ እና ስነ-ልቦናቸውን በመንከባከብ ሁለንተናዊ ተሣትፏቸውን ከፍ ለማድረግ  ታስቦ  በሰለጠኑ ባለሙያዎች የሚከናወን ተግባር ነው፡፡

“የአካል ተሃድሶ ማዕከል“ማለት የሰዎችን የተጐዳ አካል መልሶ የማስተካከል ተግባር የሚከናወንበት፣ ሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ ወይም ሰውሰራሽ እጅ እግር የሚመረትበትና አካልን የማሸት ወይም የፊዚዮቴራፒ ህክምና እና ስልጠና እንዲሁም የሥነ-ልቦና ምክር አገልግሎት የሚሰጥበት  ተቋም ነው፡፡

በክልላችንበደሴና ባህርዳርላይ እንደሚገኙ ከላይ የተመላከተ ሲሆንየተቋቋሙበት ዋና አላማም በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ በሰው ሰራሽ አደጋና በተፈጥሮ ምክንያት የተለያዩ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ከጉዳታቸው ጋር የተያያዘ ሁለንተናዊ የአካል ተሀድሶ አገልግሎቶችን ያለአንዳች ልዩነት በመስጠት ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸውን ከፍ ማድረግ ነው፡፡

Partners

Contact Us

Please write your name
Please write your e-mail address
Please write your massage
Scroll to Top